Siirry suoraan sisältöön
Life Shaped By Wisdom
Tallenna

Life Shaped By Wisdom

Kirjailija:
pokkari, 2012
amhara

"ማንም ጥበብ ቢጎድለው ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን ለእርሱም ይሰጠዋል" (ያዕ 1፥5)

የጥበብ ጉድለት ማሰብ የማይገባንን እንድናስብና መኖር የማይገባንን እንድንኖር ያደርገናል። ኑሮን ያለ ጥበብ ለመኖር መሞከር መኪናን ያለ ነዳጅ ለመንዳት እንደመሞከር ነው። አብዛኛውን ጊዜ በኑሮ ውስጥ የሚጎድለን ገንዘብ፣ ጓደኛ፣ ስራ፣ እውቀት፣ ዕድል ይመስለናል። በእርግጥ እነዚህ ነገሮች ሲጎድሉን ቶሎ እናውቃቸዋለን። ጥበብ ሲጎድለን ግን ቶሎ አንነቃም። ይህ ብቻ ሳይሆን የጎደለን ጥበብ መሆኑን ስለማናውቅ ቶሎ ብለን ሌላ ነገር እንደጎደለን እናስባለን።

ሰው ገንዘብ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው ገንዘቡ አይበቃውም፤ ጓደኛ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው የብቸኝነት ስሜት ተጠቂ ይሆናል ወይም የተሰጡትን ሰዎች በአነጋገርና በግንኙነት አያያዝ ጉድለት ያጣቸዋል፤ ስራ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው በሚያደርገው ነገርና በውሎው ድካም እንጂ እርካታ አይሰማውም፤ ዕድል ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው ችግርና ተራራ እንጂ ደረጃና ተስፋ አይታየውም፤ የሚወደዱ ውጤቶች የማይወደዱ መንገዶች እንዳሏቸው ባለማስተዋል ያለ መንገድ መዳረሻ በመፈለግ ይባክናል። ስለዚህ የጥበብ ጉድለት ያለንን ሁሉ የሌለን ያደርግብናል።

በዚህ መጽሐፍ ልዩ ልዩ የጥበብ ገጽታዎችና አሠራሮች እጅግ ሰፊ በሆነ ሁኔታ ተተንትነዋል። ኑሮአችንን በጥበብ እንድንኖር በዚህ መጽሐፍ ይህ እውነት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ንጽጽር ከብዙ ምሳሌዎች ጋር ቀርቧል። በማንበብ ራስዎን ይጥቀሙ፤ ከዚያም ቤተሰብዎንና ቤተክርስትያንን ይጥቀሙ።

Kirjailija
Ermias Tilahun
ISBN
9781087879697
Kieli
amhara
Paino
268 grammaa
Julkaisupäivä
10.4.2012
Kustantaja
Indy Pub
Sivumäärä
194