Gå direkt till innehållet
Life Shaped By Wisdom
Spara

Life Shaped By Wisdom

Författare:
pocket, 2012
Amhariska

"ማንም ጥበብ ቢጎድለው ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን ለእርሱም ይሰጠዋል" (ያዕ 1፥5)

የጥበብ ጉድለት ማሰብ የማይገባንን እንድናስብና መኖር የማይገባንን እንድንኖር ያደርገናል። ኑሮን ያለ ጥበብ ለመኖር መሞከር መኪናን ያለ ነዳጅ ለመንዳት እንደመሞከር ነው። አብዛኛውን ጊዜ በኑሮ ውስጥ የሚጎድለን ገንዘብ፣ ጓደኛ፣ ስራ፣ እውቀት፣ ዕድል ይመስለናል። በእርግጥ እነዚህ ነገሮች ሲጎድሉን ቶሎ እናውቃቸዋለን። ጥበብ ሲጎድለን ግን ቶሎ አንነቃም። ይህ ብቻ ሳይሆን የጎደለን ጥበብ መሆኑን ስለማናውቅ ቶሎ ብለን ሌላ ነገር እንደጎደለን እናስባለን።

ሰው ገንዘብ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው ገንዘቡ አይበቃውም፤ ጓደኛ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው የብቸኝነት ስሜት ተጠቂ ይሆናል ወይም የተሰጡትን ሰዎች በአነጋገርና በግንኙነት አያያዝ ጉድለት ያጣቸዋል፤ ስራ ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው በሚያደርገው ነገርና በውሎው ድካም እንጂ እርካታ አይሰማውም፤ ዕድል ኖሮት ጥበብ ሲጎድለው ችግርና ተራራ እንጂ ደረጃና ተስፋ አይታየውም፤ የሚወደዱ ውጤቶች የማይወደዱ መንገዶች እንዳሏቸው ባለማስተዋል ያለ መንገድ መዳረሻ በመፈለግ ይባክናል። ስለዚህ የጥበብ ጉድለት ያለንን ሁሉ የሌለን ያደርግብናል።

በዚህ መጽሐፍ ልዩ ልዩ የጥበብ ገጽታዎችና አሠራሮች እጅግ ሰፊ በሆነ ሁኔታ ተተንትነዋል። ኑሮአችንን በጥበብ እንድንኖር በዚህ መጽሐፍ ይህ እውነት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ንጽጽር ከብዙ ምሳሌዎች ጋር ቀርቧል። በማንበብ ራስዎን ይጥቀሙ፤ ከዚያም ቤተሰብዎንና ቤተክርስትያንን ይጥቀሙ።

Författare
Ermias Tilahun
ISBN
9781087879697
Språk
Amhariska
Vikt
268 gram
Utgivningsdatum
2012-04-10
Förlag
Indy Pub
Sidor
194